
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርኃ ግብር ተከናወነ።
የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርኃ ግብር ተከናወነ።
17/06 /2017 ዓ.ም
****አዲስ አበባ****
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀትና ተሞክሮ ሽግግር የሚካሄድበት የወርቃማ ሰኞ ማለዳ ፕሮግራም ሠራተኛውን የሚነቃቃና ለስራ ዝግጁ የሚያደርግ መሆኑ ተገለፀ።
በመድረኩ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ያለፈውን ሳምንት ውጤታማ ስራዎችን አስታውሰው የተያዘው ሳምንት የስራ አቅጣጫዎችን ሰጥተዋል።
ይህ የወርቃማ ሰኞ ማለዳም በአመራሩና በሰራተኛው መካከል ያለውን ቤተሰባዊነት እጅግ እያጠናከረና ምቹ የስራ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሚገኝ አስታውሰዋል።
በዛሬው መድረክም የባለስልጣኑ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ይልማ በራስ የመተማመን /self confidence / በተመለከተ እውቀታቸውን በማካፈል የህይወትና የስራ ተሞክሯቸውን አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments