ባለስልጣኑ ለ6ተኛ ዙር ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስል...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ ለ6ተኛ ዙር ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ከኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ።

ባለስልጣኑ ለ6ተኛ ዙር ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ከኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ።

                       17/06/2017
                   ****አዲስ አበባ****

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በ6ተኛ ዙር ለሚያሠለጥናቸው 2ሺህ የፓራ-ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ውል ስምምነት ተፈራረመ::

ስልጠናው የሚሰጠው በኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርስቲ አፓስቶ ካምፓስ እንደሚሰጥ በውል ስምምነቱ ወቅት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ አስታውቀዋል።

የፓራ ሚሊተሪ እጩ ኦፊሰሮቹ ስልጠና የንድፈ ሀሳብና ወታደራዊ ስልጠናዎችን ያካተተ እንደሚሆንና ብቁ የደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮችን በማሰልጠን ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ የኢትዮጵያ ፓሊስ ዩንቨርሲቲ ምክትል ፕሬዘዳንት ረ/ኮሚሽነር ደረጀ አስፋው ገልፀዋል።

በውል ስምምነት ፊርማው ወቅት የሁለቱም ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል ኃላፊዎቹ ተፈራርመዋል።

ከዚህ ቀደም ዩንቨርስቲው የ5ተኛ ዙር የፓራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮችን ስልጠና እና የአጠቃላይ ኦፊሰሮችን የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን መስጠቱ ይታወሳል።

ዘገባው :- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው፡፡


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments