
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ እየሰጡ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ግንዛቤ እየሰጡ ነው።
የካቲት 20/2017 ዓ.ም
****የአዲስ አበባ****
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር "የወንዝ ዳርቻ ልማት እና ብክለት መከላከል" በሚል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ጉርድ ሾላ በሚገኘው በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ቢሮ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተጀመረ።
በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው መክፈቻ ፕሮግራም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮችና ተገኝተዋል።
በስልጠናው የደንብ ቁጥሩ የሚያስተገብሩት የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች የባለስልጣኑ የቅድመ መከላከልና የመስክ ክትትል፣ ቁጥጥር ኦፊሰሮች፣ባለሙያዎች፣ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
መረጃው ፦ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments