ባለስልጣኑ የአዲስ አበባ ወንዞችና የወንዞች ዳር...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ የአዲስ አበባ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ከብክለት ፀድተው የመዝናኛ ስፍራዎች እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑ ገለፀ

ባለስልጣኑ የአዲስ አበባ ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ ከብክለት ፀድተው የመዝናኛ ስፍራዎች እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑ ገለፀ
        
                 06/07/2017 ዓ.ም
             ****አዲስ አበባ****

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር  ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን  በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት  3,669,000 / ሦስት  ሚሊየን ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት  በመቅጣት  አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በየካ ክፍለ ከተማ 2,554,000 ብር፣በአራዳ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር፣በለሚኩራ ክፍለ ከተማ 450,000ብር ፣በልደታ ክ/ከተማ 50,000 ብር እና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 15,000 ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ማድረጉን ገልጿል።

በአጠቃላይ በዛሬው እለት ደንብ የተላለፉ 10 ድርጅቶች እና
8 ግለሰቦች በድምሩ 3,669,000 / ሦስት  ሚሊየን ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሺህ/ብር በመቅጣት  አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

ባለስልጣኑ የአዲስ አበባ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ ከብክለት ፀድተው የመዝናኛ ስፍራዎች እስኪሆኑ የግንዛቤና ህግ የማስከበሩ ስራ አጠናክሮ  አንደሚቀጥል አስታውቋል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments