ባለስልጣኑ በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀው የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት 300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
ባለስልጣኑ በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀው የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት 300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
ጥቅምት 03/2018 ዓ/ም
**አዲስ አበባ**
በአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በካይ የፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቀው የፍል ውሃ አገልግሎት ድርጅት የ300 ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ ።
ድርጅቱ ፍሳሽ ቆሻሻን ባልተገባ መንገድ ወደ ወንዝ ሲለቅ በመገኘቱ ቅጣቱ ተላልፎበታል ።
ባለስልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወንዞች ዳርቻ ልማትና ብክለትን ለመከላከል በወጣው ደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት ጠንካራ ክትትል በማድረግ
አስታውቋል ።
ባለስልጣኑ ተቋማትና ግለሰቦች ማንኛውም አይነት ቆሻሻ ወደ ወንዝና የወንዞች ዳርቻ ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ እያሳሰበ ደንብ የሚተላለፉ ግለሰቦችና ተቋማትን እንደማይታገስና እርምጃውንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል፡፡
መረጃው ፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments