ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር መድረ...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር መድረክ የግጭት ማስተዳደር ስልትን እውቀት አጋራ

ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ የእውቀት ሽግግር መድረክ የግጭት ማስተዳደር ስልትን እውቀት አጋራ

  10/02/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሰኞ ማለዳ ከስራ ገበታ በፊት የሚያካሂደው የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም ግጭትን የማስተዳደር ስልት(conflict management styles) በሚል ርዕስ የባለስልጣኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት እውቀትና ልምድ ተጋርቷል፡፡

የመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ሰራተኛው ጤታማ ስራ በየሳምንቱ ከሰራተኞቻችን ጋር እንደቤተሰብ እየተማማርን መልካም ምኞት በመለዋወጥ እርስ በእርሳችን ምንማማርበት፣ ልምድ የምንለዋወጥበትና የተቋም ግንባታችን የምናጠናክርበት  መድረክ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል ።
በዕለቱ የባለስልጣኑ በባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክተር ኮለኔል አድማሱ ተክሌ በሀገር መከላከያ ሰራዊት ካላቸው ረጅም ልምድ በመነሳት የራሳቸውን የህይወት እና የስራ ተሞክሮና ልምዳቸውን ለሰራተኞች አስተማሪ በሆነ መልኩ አጋርተዋል።

በተጨማሪም ኮለኔል አድማሱ ግጭትን የማስተዳደር ስልት ( conflict management styles )በሚል ለሰራተኛው በተዘጋጀ በሰነድ እውቀት አጋርተዋል ።

ግጭትን አንዱ በሌላው ድርጊት ወይም ግቦች የራሱን ጥቅም አደጋ ላይ ይጥላል ብሎ በሚያምንበት ጊዜ በተለያዩ ወገኖች መካከል የሚፈጠር አለመጣጣም መሆኑ በሰነዱ ተገልጿል ።

ራስን ሁል ጊዜ በዕውቀት ማዳበር ፣ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ጋር መልካም ግንኙኘት መኖር እንደሚገባና ስራን በትብብር  በአንድነት  መስራት ዉጤታማ እንደሚያደርግ በመድረኩ ገልጸዋል ፡፡

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ  የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments