ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስ...

image description
- In code inforcement    0

ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስጠት የውል ስምምነት አካሄደ ።

ለባለስልጣኑ አመራር እና ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስጠት የውል ስምምነት አካሄደ ።          
         
                25/02/2018 ዓ.ም
                 **አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ለአመራሮችና ለኦፊሰሮች የአጭር ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ጋር የባለስልጣኑ እና የዩኒቨርስቲው አመራሮች በተገኙበት የውል ስምምነት ፊርማ አካሄደ ።

በስምምነቱ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ከፍያለው ታደሰ አመራሩና ኦፊሰሩ አቅም ለማሳደግ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ዩንቨርስቲው ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል ።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በበኩላቸው ተቋሙ እና ከተማው የሰጣቸው ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል ስልጠና ልምድና እውቀቱ ባላቸው አሰልጣኞች እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments