ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን በሰላም እንዲ...

image description
- In code inforcement    0

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለፀ

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለፀ

             12/09/2018 ዓ.ም
               **አዲስ አበባ**   

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቅድመ ምርጫ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት የተቀናጀና የተጠናከረ የጥበቃና የሰላም ግንባታ ተግባራትን በማከናወን ሰላማዊ ምርጫ እንዲከናወን የውይይት መድረክ አካሄደ ።

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ  እጅግ ሰላማዊ ፣ ነጻ ፣ ፍትሀዊና ተዓማኒ  በማድረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሻገር እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልጸዋል ።

አክለውም የደንብ ማስከበር አመራርና ኦፊሰር ምርጫው በከተማችን በሰላም እንዲጠናቀቅ  ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙ ሲሆን ይሄንንም በቀጣይ በምርጫ እለት እና በድህረ ምርጫ ወቅት አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

ለሀገራችን ሰላም እና ደህንነት በጋራ መቆም እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል ።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments