በህብረተሰቡ የሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥና የመል...

image description
- In code inforcement    0

በህብረተሰቡ የሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ።

በህብረተሰቡ የሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት  በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ።
               13/09/2018 ዓ.ም
               ****አዲስ አበባ****    

የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን  በደንብ ቁጥር 150/2015 ለማስፈጸም በወጣ የአፈጻጸም መመሪያ 2/2015 ላይ ለከተማው ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ  አካሂዷል ። 

በመድረኩ የባለስልጣኑ ም/ስራ አሰኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ከህብረተሰቡ የሚሰጡ ግብዓቶችን ወደ ተቋሙ እቅድ በማካተት ስራዎች በጋራ መሰራታቸውን በመግለጽ በቀጣይም ህብረተሰቡ ከደንብ ማስከበር ጋር ያለውን ቅንጅት አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ። 

አክለውም ተቋሙ በተለያዩ ወቅቶች ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በስፋት በመስራት ከመቅጣት በፊት አስቀድሞ የደንብ መተላለፎች የመከላከል ስራን በማከናወን በከተማችንን የደንብ መተላለፍ እንዲቀንሱ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል ። 

ባለስልጣኑ ከተሰጠው ተልዕኮ ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድ ሰው ተኮር ሰራዎችን በማከናወን ወላጆቻቸው ያጡ ህጻናትን መንከባከብና መደገፍ እንዲሁም አስራ ሰባት የአቅመ ደካማ ቤት በተለያዩ ክ/ከተማዎች ገንብቶ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ ማስረከቡ ተገልጿል ። 

በመድረኩ ተቋሙ ሪፎርም በማድረግ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ባለስልጣኑ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል ። 

በመጨረሻም ከመድረኩ ተሳታፊ ህብረተሰብ ውይይት በማድረግ የተቋሙ የሪፎርም ስራዎች በማስጎብኘት ህብረተሰቡ ተቋሙን በማገዝ የደንብ መተላለፎች በከተማው እንዲቀንስ የራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡ ተጠይቋል።

ዘገባው፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments