የባለስልጣኑ ስኬቶች ድንገተኛ ሳይሆን በትጋትና...

image description
- In code inforcement    0

የባለስልጣኑ ስኬቶች ድንገተኛ ሳይሆን በትጋትና የመስራትና የስትራቴጄክ ዕቅድ ሥራዎች ውጤት መሆኑ ተገለፀ

የባለስልጣኑ ስኬቶች ድንገተኛ ሳይሆን በትጋትና የመስራትና የስትራቴጄክ ዕቅድ  ሥራዎች ውጤት መሆኑ ተገለፀ   

13/11/2018

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 በጀት ዓመት በተካሄደው የተቋማት የሥራ አፈፃፀም ምዘና (ካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት) ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም አንደኛ ደረጃ በመያዝ የላቀ ስኬቱን አስመዝግቧል።

ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ታላቅ ድልና ስኬት ከተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች ጋር በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ በማክበር ስኬቱ ማስቀጠል የሚቻልበት ስልተ ተመላክቷል።

​የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በመድረኩ እንደገለጹት፣ “ይህ ተከታታይ እና ወርቃማ ድል ሊገኝ የቻለው ከላይ እስከ ታች ባለው ሙሉ የአመራር፣ የሰራተኛና የፖራ ሚሊተሪ ኦፊሰሮች ያልተቆጠበ ጥረት፣ የተቀናጀ አሰራር፣ የላቀ የቡድን መንፈስ እና ለከተማችን ያለን ከፍተኛ ፍቅር ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ!” ብለዋል።

​የባለስልጣኑ ስኬቶች ድንገተኛ ሳይሆን በትጋትና በዕቅድ የመራናቸው ሥራዎች ውጤት ናቸው ፤በ2018 በጀት ዓመት ያስመዘገብነው አንደኛ ደረጃ ከተማ አስተዳደሩ የተጣለብንን አደራ በብቃት መወጣታችንን የሚያረጋግጥ መሆሁ ገልፀዋል።

በቀጣይም ይህንን የስኬት ጉዞ ሳናቋርጥ የከተማችንን የደንብ ማስከበር ሥራ ይበልጥ በማዘመንና የደንብ ጥሰቶችን በመቀነስ የተገኘውን ድል አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ ገልጸዋል ።

​በዕለቱ የደስታው ተካፋይ የሆኑት የባለስልጣኑ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ሰራተኞችና ኦፊሰሮች በተገኘው አንጸባራቂ ውጤት የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸው፣ የተጀመረውን ውጤታማ የጋራ አሰራር በቀጣይም አጠናክረው ለማስቀጠል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments