
የአንካራው ስምምነት የተገኘው ውጤት የሀገራችን ጠንካራ የዲፕሎማሲ ውጤት ማሳያ መሆኑን ተገለፀ
የአንካራው ስምምነት የተገኘው ውጤት የሀገራችን ጠንካራ የዲፕሎማሲ ውጤት ማሳያ መሆኑን ተገለፀ
07/04/2017 ዓ.ም
****አዲስ አበባ****
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የማዕከል፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ኃላፊዎች እእንዲሁም የማዕከሉ ዳይሬክተሮች በተገኙበት በወቅታዊ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የተደረሰውን የአንካራ ስምምነት ተከትሎ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
የውይይቱ መነሻ ሰነድ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ ቤት የአቅም ግንባታ እና የፖለቲካ ዘርፍ ምክትል ሀላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ የአንካራው ስምምነት የተገኘው ውጤት የሀገራችን ጠንካራ የዲፕሎማሲ ውጤት ማሳያ መሆኑ ገልፀዋል።
በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ተፅኖ ፈጣሪነት ለማሳጣት በጎረቤት ሀገራት በጠላትነተ ለማስፈረጅ የየተዘጋጁ አካላት ሴራ ያከሸፈ መሆኑ ገልፀዋል።
አክለውም ስምምነቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ጥበብና ብስለት በተሞላበት መንገድ ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ በህጋዊ መልኩ ምላሽ የተገኘበት መሆኑ ገልፀዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በአንካራው ስምምነት በርካታ የኢኮኖሚ ትሩፋቶች የሚያስገኝ በመሆኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል የሀገራችን ብልፅግና እውን ለማድረግ የሚያጠናክር መሆኑ ገልፀዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments