
ባለስልጣኑ የህዝብና የመንግስትን መሬት የወረረን ግለሰብ ተጠያቂ ማድረጉን አስታወቀ
ባለስልጣኑ የህዝብና የመንግስትን መሬት የወረረን ግለሰብ ተጠያቂ ማድረጉን አስታወቀ
ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም
****አዲስ አበባ****
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ቦታው ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ቶልቻ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሬት ባንክ የገባን የህዝብና የመንግስትን መሬት በህገወጥ መንገድ ለግል ጥቅም ለማዋል የተወረረን መሬት ማስመለሱ አስታውቋል።
ግለሰቡ በሌሊት ጨለማን ተገን በማድረግ 477.61ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ቦታ በማጠር የወረረ መሆኑን በባለስልጣኑ የለሚኩራ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር አባላቱ በተደረገው ክትትል የተደረሰበት መሆኑ ተጠቁሟል።
ባለስልጣኑ መረጃውን በማጣራት ከፖሊስ አባላት ጋር በመሆን ግለሰቡን በቁጥጥር ስር በማዋል በሊዝ አዋጅ ተጠያቂ እንዲቀጣ ክስ እንዲመሰረት በማድረግ የታጠረውን ቦታ በማፍረስ ወደ ነበረበት እንዲመለስ ማድረጉ ገልጿል።
ባለስልጣኑ በህገ ወጦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፀ ሲሆን ደንብ የሚተላለፉ አንዳንድ ግድ የሌሽና ስግብግብ ግለሠቦችን ልማት ወዳዱ የከተማችን ነዋሪዎች በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪውን ያቀርባል ።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments