
ባለስልጣኑ የሚሰጠውን አገልግሎትና ተግባራቶቹን ቴክኖሎጂ ለመጠቀም በማስፈፀሚያ እቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ
ባለስልጣኑ የሚሰጠውን አገልግሎትና ተግባራቶቹን ቴክኖሎጂ ለመጠቀም በማስፈፀሚያ እቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ
30/04/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አገልግሎትና ተግባራቶቹን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የሚያስችል አጭር የማስፈፀሚያ እቅድ የባለስልጣኑ ፕሮሰስ ካውንስል አባላትና እና ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ከተወከሉ የሶፍትዌር እና የፕሮጀክት ቡድን መሪዎቸሸ ጋር ውይይት ተካሄደ ::
በውይይቱ ባለስልጣኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማተሸን ለመሠዘመን ባስቀመጠው አቅጣጫን መሰረት ለተገልጋይ እና ለአገልጋይ ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር ተቋሙን ከዘመኑ ጋር ለማራመድ ስራዎቸሸ መጀመራጀው የባለሥልጣኑ ዋና ስራአስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል::
አክለውም ተቋሙ የእቅዱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ግልፅ አሰራር ለመዘርጋት፣ ከወረቀት ነፃ አገልግሎት ለመስጠት፣ የመረጃ አያያዝ በማዘመን ደንብ መተላለፍና ተያያዥ ህገ-ወጥ ተግባራትን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር እንዲሁም ብልሹ አሰራርን በመቀነሰ የተገልጋይን እርካታ ለመጨመር የሚረዳ አሰራር ስርአት ቴክኖሎጂ ለመዘርጋት መታቀዱ ጠቁመዋል::
ማስፈፀሚያ እቅዱን ያቀረቡት የባለስልጣኑ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ በተቋሙ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማትን ለመገንባት በካሜራና በሶፍትዌር የታገሰ የአገልግሎትና የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት የማስፈፀሚያ እቅዱ መዘጋጀቱን ገልፀዋል::
በቀረበው እቅድ ላይ ተሳታፊዎች ስራዎችን በቴክኖሎጂ ከማዘመን እና ከማቀላጠፍ አኳያ አዳዲስ በሚያስፈልጉ እና ሌሎች ትኩረት በሚያስፈልጋቸው ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጓል::
በመጨረሻም የባለሥልጣኑ ዋና ስራአስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሌሎች ተቋማት በደረሱበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም የዕድገት ደረጃ መድረስ ያስችለው ዘንድ የባለድርሻ አካላትን በዘርፍ ያላቸውን እውቅት፣ ልምድና ተሞክሮ በመወሰድ የሚጀመርበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/
የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement
የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT
የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen
ለማንኛውም የደንብ መተላለፍ ጥቆማ ነፃ የስልክ መስመር 9995 ይጠቀሙ
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments